CHARITY
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር
ከ “እኔም ለሀገሬ በሀምፕተን ሮድስ ቨርጂኒያ” አባላት
በተደረገ የገንዘብ ድጋፍ 6ኛውን የሕክምና ጉዞ ወደ ወልድያ
ጥር 21-23/ 2014 ዓ.ም
በዚህ አገልግሎት ከተለያዩ የጤና ሙያ የተውጣጡ 48 ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። ጠቅላላ ሐኪሞች፣ የውስጥ ደዌ፣ የልብ፣ የህጻናት፣ የዐይን እና የስነ-አዕምሮ ስፔሻሊስቶች፣ ነርሶች፣ ፋርማሲስቶች፣ ላቦራቶሪ ቴክኒሻኖች እና ሌሎችም ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
በጠቅላላው ለ 1,644 ታካሚዎች አገልግሎት ለመስጠት ተችሏል።
➊ የውስጥ ደዌ ሕክምና ያገኙ፡ 813
➤ የልብ ሕክምና፡ ከ 50 በላይ
➤ የልብ አልትራሳውንድ (Echocardiogram) የተሰራላቸው፡ 47
➤ የልብ ሰርጀሪ የሚያስፈልጋቸው፡ 4 ታካሚዎች ተለይተዋል
➤ ለከፍተኛ ህክምና በሪፈራል የተላኩ እና በሆስፒታሉ በመተኛት ሕክምናቸውን እንዲቀጥሉ የተደረጉ፡ 5
➋ የህጻናት ሕክምና ያገኙ፡ 259
➌ የዐይን ሕክምና ያገኙ፡ 347
➤ የተለያዩ የዐይን ሕክምና መስጫ መሳሪያዎችንና መድኃኒቶችን ለሆስፒታሉ የዐይን ክፍል ለግሰናል
➍ የስነ-አዕምሮ ሕክምና ያገኙ፡ 156
➤ በሆስፒታሉ የስነ-አዕምሮ ክፍል በመተኛት ሕክምናቸውን እንዲቀጥሉ የተደረጉ፡ 2 ታካሚዎች
➎ የተሟላ የላቦራቶሪ ምርመራ ተካሂዷል
➏ አስፈላጊ መድኃኒቶች ለሁሉም በነጻ ታድሏል
➐ 2,400 ካርቶን አልሚ ምግብ በምግብ እጥረት ለተጠቁና ተጋላጭ ለሆኑ ህጻናትና እናቶች አድለናል።
ለዚህ የሕክምና ጉዞ መሳካት በገንዘብ ላገዙን “እኔም ለሀገሬ በሀምፕተን ሮድስ ቨርጂኒያ” አባላት በአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ስም ምስጋና እናቀርባለን። የወልድያ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ላደረጋችሁልን ትብብር እናመሰግናለን። በዚህ አገልግሎት ላይ የተሳተፋችሁ የጤና ባለሙያዎችና የኢ.ኦ.ተ.ሕ.ማ. አባላት በሙሉ በእግዚአብሔር ስም እናመሰግናለን።
ኢ.ኦ.ተ.ሕ.ማ. የሁሉም በሁሉም !
EOTMA for all by all !